Wednesday, August 28, 2013

አዲስ አበባ እንደወንዝ



   ባለፉት ተከታታይ ቀናት አመሻሹን በዘነበው ዝናብ ምክንያት የአዲስ አበባን መንገዶች ውሃ ሞልቷቸው ነበር፡፡ የከተማዋ በየቦታው መቆፈርና መታረስ የትራንስፖርት ችግር ከማስከተሉም ባሻገር መንገገዶቿም ወንዝ እንዲሆኑ አስገድዷቸዋል፡፡ በተለይ የካቲት 16 የዘነበው ኃይለኛ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ የመላው አፍሪካ ሃገራት የወንዝ ኤግዚብሽን በአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ እየተካሄደ ያለ አስመስሎታል፡፡ 
   በውሃ የተጥለቀለቁት መንገዶች ፈርሰው እየተገነቡ ያሉት ብቻ ቢሆኑ አያስገርምም፡፡ ይልቅስ አዳዲሶቹና ዘመናዊ የተባሉትም መንገዶች ወንዝ የሆኑ ይመስላል፡፡ በየጊዜው የሚለፈፍ ቢሆንም አሁንም የከተማዋን የፍሳሽ አወጋገድ ሥርዓት አንኳር ጥያቄ ውስጥ የሚዶል ነው፡፡ የፍሳሽ ማስወገጃ ቦዮች በሙሉ በሚያሰኝ አኳኋን የታሸገ ውሃ መያዣ ላስቲክና የጫት ትራፊ ሞልቷቸዋል፡፡ ተጠቃሚውም አጥፊ ሰሪውም ግድ የለሽ፡፡ በዛ ላይ አብዛኞቹ መንገዶች በመታጠራቸው ጠበዋል፡፡ መጥበባቸው ብቻ አይደለም ጉዳቱ ሰዎች እንደ እንቁላል እየተነሱ ይፈርጡበታል፡፡ ድሮ ሰው ሲወድቅ “አከሌ መሬት ገዛ” ተብሎ ይቀለድ ነበር፡፡ አሁንስ? ‘ሊዙን’ ማን ይችለዋል? ባይወደቅ ቢቀርስ!
   እነዚህ እየተገነቡ ያሉት መንገዶች ለሁለት ጥቅም ታስበው ተሰርተው እንደሆን ለሰፊው ሕዝብ ቢገለፅ ውብ ነበር፡፡ ነገር ግን አልተነገረውም፡፡ ቢነገረው አቅም ያለው አነስተኛ ጀልባ ይገዛል አልያም ይከራያል፡፡ የሌለው ደግሞ ቦት ጫማ ለመግዛት አያንስም ነበር፡፡ በቆዳ በሸራና በስኒከር ጫማዎች የአዲስ አበባን መንገዶች መጓዝ ጦሱ ላፍንጫ ነው፡፡ አሁን የአዲስ አበባን መንገዶች እንደወንዝ እንጂ እንደሌላ ማሰብ እንዴት ይቻላል? በትልልቅ አለቶችና አሸዋ የተሞላን መንገድ ወንዝ እንጂ ምን ይሉታል? በተለይ እንደ ገበጣ መጫዎቻ የተፈነካከተውን ከቃሊቲ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አንስቶ እስከ ቃሊቲ ቶታል ያለውን አስፓልት መሳይ ያየ መንገዶቻችን እንዴት ባለ ጥራት እንደሚገነቡ ያስተውላል፡፡ 
   በነገራችን ላይ አልሰማሁ ይሆናል እንጂ ባለፈው ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ከተመራጮች አንዱ ወይ ሁለቱ እንዲህ ብለው ከነበረስ ‹‹የአዲስ አበባን ሕዝብ የወንዝ ፍላጎት ለሟሟላት መንገዶች ሁሉ ወንዝ እንዲሆኑ የወንዞቹን ቁጥር በእጥፍ እናሳድጋለን፡፡ ለዚህም ስኬት እጅ ለእጅ ተያይዘን የምንሰራበት  ሂደት ነው ያለው፡፡›› ተሳክቶላቸዋል፡፡ ድጋሚ እንመርጣችኋለን እኛ የወንዝ አምሮታችን የወጣልን አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፡፡ 

Tuesday, August 20, 2013

ፍልሰታ ለማርያም ክፍል ሁለት





እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አርጋለች ወደ ገነት
እመቤቴ ማርያም ሆይ፤ ምጡቅና ሩቅ ወደሚሆን የደስታ ቦታ ላረገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል 
 ይኸውም ኅብሩ ሊመረምሩት በማይቻል ዕንቊ የታነፀ ሕንፃ ይገኝበታል፡፡
መልክአ ማርያም
ቅዱሳን ሐዋርያት፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከእነርሱ በመለየቷ ፈጽመው ያዝኑ ነበር።  ከእለታት በአንዱ ቀን ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያቱ ተገለጠላቸውና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እንደሚያዩ ተስፋ ሰጣቸው።  በዚያን ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌልን እየሰበከ፤ እያስተማረ፤ ሕዝበ ክርስቲያንን እያጽናና እስያ በምትባል ሃገር ነበር።  ከዚያም በመንፈስ ቅዱስ ተነጥቆ፤ ተድላና ደስታ ከሰፈነባት ቦታ ወደ ገነት ሄደ።  ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ሥር ተቀምጦ አየው።  የንጽሕት አናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሯት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው። ቅድሳን መላእክቱም  እንደታዘዙት አደረጉ። ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ወጣ።  ጌታችንም

Thursday, August 15, 2013

የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፈተና ውስጥ መሆኗን ክርስቲያኖች ገለጹ



  በኤርትራ የክርስቲያኖች መከራ ወደከፋ ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑን ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ የኤርትራ ቤተክርስቲያን መሪዎች ኦፕን ዶርስ ኢንተርናሽናል ለተባለ የክርስቲያን ግብረ ሠናይ ድርጅት መናገራቸውን ዘኦርቶዶክስ ቸርች ዶት ኢንፎ የተባለ ድረ ገጽ አስነብቧል፡፡ ከአዲቀዪ የሥነጥበብና ማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ 31 ተማሪዎችንና ከአስመራ ሕያው እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ተይዘው የተወሰዱትን አምስት ሰዎች ጨምሮ በዚህ ዓመት ብቻ በመንግስት ተይዘው የታሰሩት ክርስቲያኖች ቁጥር 191 መድረሱም ተመልክቷል፡፡
  ከዚህ ጋር በተያያዘ የኤርትራ መንግሥት ክርስቲያን የሆኑ እስከ ሦስት ሺሕ ሰዎችን እንዳሰረ የሚገመት ሲሆን ከነዚህ ውስጠ ፓትርያርኩ አቡነ አንቶኒዮስ ይገኙበታል፡፡ በዚህም ምክንያት የኤርትራኦ ርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አገልግሎት ከጊዜ ወደጊዜ እየተዳከመ ነው፡፡ በሰብአዊ መብት ጥሰት ዘወትር በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ሪፖርት የሚወጣበት የኤርትራ መንግሥት ግን ክሶቹ ሁሉ መሠረተቢስና የተቀነባበሩ ናቸው ሲል ባገኘው አጋጣሚ መልስ እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ በኤርትራ ግማሽ ያሁሉ ሕዝብ ክርስቲያን ሲሆን ከክርስቲያን ማኅበረሰቡ ደግሞ ከአሥሩ ዘጠኙ የኦርቶዶክስ ክርስትና ሃይማኖት የሚከተሉ እንደሆነም ተመልክቷል፡፡

ምንጭ፡ ሐመር መጽሔት ሐምሌ 2005 ዓ.ም.

Tuesday, August 13, 2013

ፍልሰታ ለማርያም




ምንጭ፡ www.ermiasnebiyu.org
ክፍል አንድ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ከመሞቷ በፊት በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መቃብሩ ቦታ ትጸልይ ነበር።  መንፈስ ቅዱስም ለእመቤታችን ከዚህ ዓለም እንደምትለይ ነገራት።   ጌታችንም በደብረ ዘይት ላሉ ደናግላን ነግሯቸዋልና ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በፍጥነት መጡ።  እርሷን መንፈስ ቅዱስ የነገራትን ነገረቻቸው።  እነሱም እንደመጡ ባየች ጊዜ እንዲህ ብላ ጸለየች። ‹‹ልጄ ወዳጄ፤ ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናየን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚህች ሰዓት አምጣው፤ እንዲሁም በሕይወት ያሉትንና በሕይወት የተለዩንን ቅዱሳን በሙሉ ወደ እኔም አምጣቸው።  አንተ የሕያዋን አምላክ ነህና፤ለአንተም ምስጋና ይሁን አሜን›› አለች።  በዚያን ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትዕዛዝ ቅዱስ ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አደረሰችው።  ቅዱስ ዮሐንስም እንደደረሰ ሰገደላትና በፊቷ ቆሞ እንዲህ አላት፤ ‹‹ሰላምታ ይገባሻል ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወልደሽልናልና፤ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ።  አንቺ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘለዓለም ሕይወት ትሄጃለሽና።››  እመቤታችንም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላት እንዲህ ብላ አምላኳንም አመሰገነችው።  ‹‹ጌታዬ አምላኬ ፈጣሪዬ ሆይ፤ ላንተ ክብር ምስጋና ይገባል።  የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና።  አሁንም ነብሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊይሳርጓት ከሚመጡ መላእክቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።›› በዚህን ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ድምጽ መጣ፤ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ።  ቅዱሳን ሐዋርያትም ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ይደርሳሉ።  ቅዱሳን ሐዋርያት ከዚህ ዓለም የተለዩትም፤ በሕይወት ያሉትም ሁሉ በአንድነት መጥተው ለእመቤታችን ሰገዱላት።  እነርሱም አመሰገኗት እንዲህም አሏት።