በስመአብ
ወወልድ
ወመንፈስ
ቅዱስ
አሀዱ
አምላክ
አሜን
ደብረ ታቦር የግEዕዝ ቋንቋ
ሲሆን የታቦር ተራራ
ማለት ነው፡፡ማቴ 7፣1-8
የታቦር ተራራ የሚገኘው
አሁን ፍልስጥኤም ተብሎ በሚጠራው
ሀገር ነው፡፡ ደብረ
ታቦር ወይንም የታቦር
ተራራ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን
ይዞ ወደ ተራራው
የወጣበትና ፊቱ XEንደ ፀሐይ የበራበት ልብሱም
እንደ ብርሃን
ነጭ የሆነበት ቦታ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ከሚከበሩት ከዘጠኙ ዓበይት
በዓላት አንዱ ደብረ ታቦር
ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ
ነሐሴ 13
ቀን
በድምቀት ይከበራል፡፡ ታቦር ከገሊላ
ባሕር በምዕራባዊ
ደቡብ በኩል 10ኪ.ሜ ርቆ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡
ይህ ተራራ ከባሕር ጠለል 572
ሜትር ከፍታ አለው፡፡ «ባርቅ የተባለው ጦረኛ
ሕዝበ
እEስራኤልን ይዞ በመዝመት
ሲራ
የተባለውን የሕዝብ ጠላት
በታቦር ድል ነስቶ
አሸንፏል” መሳፍንት 4፣6-14፡፡
ልበ xምላክ ቅዱስ
ዳዊትም “ታቦርና xርሞንኤም በስምህ
ደስ ይላቸዋል፡፡ ክንድህ ከኃይል
ጋር ነው” ሲል በመዝሙር 88፣12 ስለ ታቦር
ተራራ ዘምሯል፡፡ የታቦር ተራራ
በገሊላ ከሚገኙ ተራራዎች
አንደኛው ሲሆን በዛብሎን ክፍል ውስጥ
ለሚኖሩ ልጆች የተሰጠ
ቦታ ነው፡፡ 1ኛ ዜና.6፣77 ሐዲስ ኪዳን ግን ረጅም ተራራ ከማለት በስተቀር ታቦር ብሎ ስሙን አይጠራውም፡፡ ሆኖም ክርስቶስ
በዚህ ተራራ ላይ ክብሩን እንደገለጠና የዚህም ተራራ ስም ታቦር መሆኑን
ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው ገልጠዋል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ
ያሬድም ይህንን ረጅም ተራራ ደብረ ታቦር እEያለ በድጓው አስፍቶ ጽፏል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ረጅም ተራራ
የወጣው ብርሃነ መለኮቱን
ክብሩን ለመግለጽ ነው፡፡
በዚህ ተራራ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙሴና ከኤልያስ ጋር ተነጋግሮአል፡፡እነዚህም
ሁለት ታላላቅ ሰዎች
በበብሉይ ኪዳን ጊዜ ስለ ክርስቶስ
ትንቢት የተናገሩ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ያስተማሩ ቅዱሳን
ነቢያት ነበሩ፡፡ ከነቢያት መካከል ሁለቱ
ቅዱሳን ነቢያት እEንዲገኙ ያደረገውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቂሣርያ ተገኝቶ «ደቀ
መዛሙርቱን ሰዎች እኔን ማን ይሉኛል) ሲል ጠየቃቸው
ከEነሱም አንዳንዶቹ ኤልያስ፣ አንዳንዶቹም ሙሴ፣ ነው ይሉሃል አሉት፡፡እEናንተስ ማን ትሉኛላችሁ)
ቢላቸው አብዛኛዎቹ ኅብረተሰቡ ከሚለው ጋር ሲተባበሩ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ ሲል መሰከረ፤ኢየሱስም መልሶ ይህን በሰማያት ያለው አባቴ
እEንጂ ሥጋና
ደም አልገለጠልህምና ብፁዕE ነህ አለው፡፡㹹ማቴ.16፣13-18፡፡ በዚህ አኳኋን ወደ ደብረ
ታቦር ተራራ ጴጥሮስ፣
ዮሐንስና ያዕቆብን ይዞ ወጥቶ ራሱ ኤልያስ
ወይም ሙሴ አለመሆኑን ገለጠላቸው፡፡
ከሞተ ብዙ ዘመን
የሆነውን ሙሴን ከመቃብር
አስነስቶ ቀጥሎም
በEእሳት ሠረገላ ያረገውንና በተድላ ገነት
የሚኖረውን ኤልያስን በተራራው እEንዲገኝ አድርጐ አብረውት የነበሩት ደቀ መዛሙርት
ሙሴ ነው ወይም
ኤልያስ ነው በማለት
ሲጠራጠሩ
እEንዳይኖሩ ትምህርት ለመስጠት
ነው፡፡
ማቴ.17፣2 «በፊታቸው
ተለወጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ
በራ ልብሱም እEንደ ብርሃን ነጭ ሆነም
ይላል፡፡ የክርስቶስ ፊቱ እEንደ ፀሐይ
የበራው የብርሃኑም ኃይል ያንፀባረቀው
የብሉይ ኪዳን መሪ እንደነበረው እንደ ሙሴ ፊት ብርሃን አይደለም፡፡
«ሙሴ ከሲና
ተራራ ሲወርድ የፊቱ
ቆዳ አንፀባረቀ አሮንና
እEስራኤልም ይህንን ስላዩ
ወደ
እሱ ይቀርቡ ዘንድ ፈሩ ተሸፈንም እያሉ ጮኹ «ሙሴም
እግዚአብሔር
ያዘዘውን ለEነሱ ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ
በፊቱ መሸፈኛ አደረገ ይላል፡፡ ዘፀ. 34፣29-30፡፡ የሙሴ የጸጋ
ነው የክርስቶስ ግን የባሕርይ
ነው፡፡ «ብሩህ ደመና ጋረዳቸው”
ይላል ይህ በሲና እንደታየው
ያለ አይደለም፡፡ በታቦር የታየው
ግን ብሩህ ነበር፡፡
በደብረ
ሲና የተገለጠ የፍጡር
የሙሴ ክብር ነበር፤
በደብረ ታቦር ግን የሕያው ባሕርይ የክርስቶስ ክብር ተገልጦአል፡፡
የደብረ ታቦር በዓል በቤተ ክርስቲያን በኩል ያለው አከባበር፡-
1ኛ. ደብረ ታቦር ከዘጠኙ Aበይት በዓላተ እግዚእ አንዱ ነው
ከዋዜማው ጀምሮ እስከ በዓሉ ፍጻሜ
ድረስ ማኅሌት ይቆማል፡፡
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ
ስለ በዓሉ የደረሰው
መዝሙር
ይዘመራል፡፡ «ሰበሕኩከ በደብር በቅድመ
ሙሴ ወኤልያስ ነቢያት
እEምዕመናኒከ በታማኞችህ ነቢያት በሙሴና በኤልያስ ፊት የባሕርይ
ልጅነትህን መሰከርሁልህ” የሚለው መዝሙር ለበዐሉ
ልዩ ድምቀት ስጥቶት
ይውላል፡፡
2ኛ. የደብረ ታቦር በዓል በቆሎ ተማሪዎች በኩል ያለው ይዞታ
የቆሎ ተማሪዎች በዓሉ
አንድ ወር ሲቀረው በየመንደሩ ተዘዋውረው ጥሬ በልመና
ይሰበስባሉ፤ ከለመኑትም ጥሬ ግማሹን ጠላ ይጠምቃሉ፣
ግማሹን ቆሎ ይቆሉታል፡፡
በዚህ ሁኔታ ሲዘጋጁ
ይሰነብቱና በደብረ ታቦር
እለት የለመኑትን ኅብረተሰብ የደብሩን ካህናትና
አለቃ አስተማሪዎቻቸውን ጠርተው ይጋብዛሉ፡፡
በሚጋብዙበትም
ወቅት
እEየዘመሩ ተጋባዡን ያስደስቱታል፡፡
3ኛ. የደብረ ታቦር በዓል ከኅብረተሰቡ ጋር ያለው የባህል ግንኙነት
ማንኛውም ኅብረተሰብ በዋዜማውና በዕለቱ ችቦ እያበራ ያከብረዋል፡፡ ሴቶችም በዋዜማው
እንደ ጥብኝ ወይም
ሙልሙል አድርገው ከስንዴ ዱቄት የተቦካ ዳቦ በብዛት ይጋግራሉ ወደ ቤት ሊጠይቅ ለሚመጣ ሰው ሁሉ ዳቦ
ያቀርቡለታል፡፡ በጠቅላላው ዘመድ አዝማዱ ዳቦ እየተያዘ የሚጠያየቅበት የተነፋፈቀ ሁሉ የሚገናኝበት የተራራቀ
ሁሉ የሚቀራረብበት በዓል በመሆኑ በዓሉ በኅብረተሰቡ ዘንድ ከፍ ያለ ተወዳጅነት አለው፡፡
4ኛ. የደብረ ታቦር በዓል በልጆች በኩል ያለው ሁኔታ
ወንዶች ልጆች ከዋዜማው ጀምሮ በቡድን፣ በቡድንዘ እየተከፋፈሉ ዳቦና ገንዘብ የሚቀበል ልጅ ከመካከላቸው
ይመርጣሉ፡፡ ከዚያ በኋላ በየመንደሩ
እየዞሩ የባህል ዘፈን
እEየዘፈኑና የሰጪዎችንም ስም
እEያወደሱ ዳቦና ገንዘብ
ይቀበላሉ፡፡ በEዕለቱ እEየጨፈሩ ካረፈዱ በኋላ ጨፍረው ያገኙትን ዳቦ አንድነት ተሰብስበው ይመገባሉ፡፡ ገንዘቡንም
ተከፋፍለው ለየችግራቸው ያውሉታል፡፡ የቡሄ ወይንም የደብረ ታቦር በዓል የተወደደና በጣም የሚናፈቅ ነው፡፡ የደብረ ታቦር በዓል በኅብረተሰቡና
በልጆች በኩል የሚታወቀው ቡሄ በሚል ስም ነው፡፡ አባቶች ቡሄ ማለት በራ፣ ብርሃን ማለት ነው
ይላሉ፡፡ በደብረ ታቦር የበራውን ብርሃን ያመለክተናል፡፡
ወስብሐት ለእEግዚአብሔር!

No comments:
Post a Comment