Monday, April 30, 2012

“መንግስታዊ ሃይማኖት መኖሩ ለዴሞክራሲው ግንባታ እንቅፋት ነው”



“በአፄ ኃ/ሥላሴ የንግስና ዘመን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ መስቀል በያዘ አንበሳ አርማ የተዘጋጀ ነበረ፡፡ ይህም እስልምናውን ያገለለ ለአንድ ሃይማኖት ብቻ የቆመ አገዛዝ እንደነበረ የሚያረጋግጥ ነው፡፡”
ሚያዝያ 20 ቀን 2004 ዓ.ም ምሽት በኢቴቪ የተዘጋጀ ውይይት ላይ ከእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የተወከሉ ሰው የተናገሩት፡፡

Friday, April 20, 2012

ይድረስ ለአባ ሰላማዎች

Aba Selama: ማህበረ ቅዱሳንና ሰለፊያ!! ግልባጩ ማነው? - - - Read PDF: ከአውደ ምሕረት የተወሰደ የማህበረ ቅዱሳን ሰለባ የሆኑ ብዙ የቤተክርስቲያን አባቶችና ልጆች ማቅን በአሸባሪነት ከፈረጁት ዓመታት የተቆጠሩ ቢሆንም፣ ማቅ ግን እንዲህ የሚሉኝ ለቤተ ክርስቲያን ጥብቅና ስለቆምኩ ነው በሚል ራ...


ይድረስ ለአባ ሰላማዎች
ሰሞኑን በተወካዮች ምክር ቤት የተወራው ወሬ ጮቤ ያስረገጣችሁ ይመስላል፡፡ ለደስታችሁ ወደር ለመድረሻችሁም ድንበር እንደማይገኝለት ግልጥ ነው፡፡ ምክንያቱም የምትጠሉት ማህበር፣የሚያንገሸግሻችሁ ማህበር፣መግቢያ መውጫ ያሳጣችሁ ማህበር፣ የስርቆትን በር የዘጋባችሁ ማህበር፣ከአባቶቻችሁ የተላካችሁትን እንዳታስፈጽሙ ጋሬጣ የሆነባችሁ እግር በግር እየተከታተለ ሥራችሁንና ማንነታችሁን የሚያሳብቅባችሁ ማህበር በአንድ በተከበሩ ሰው ያውም ለኛ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ስጋትና ጭንቀት ከሆነው ውሃቢዝም ጋር አጣግተው አክራሪ የሚል ቃል ስለተናገሩላችሁ እግራችሁ ከመሬት ከፍ ብሎ ጭንቅላታችሁ ከሰማይ እስኪላተም ድረስ አዘለላችሁ አስፈነደቃችሁ፡፡ እንኳን ደስ ያላችሁ፡፡

Thursday, April 12, 2012

ጸሎተ ሐሙስ


አትም ኢሜይል

በሊቀ ጠበብት ሐረገወይን አገዘ
ጸሎተ ሐሙስ ነቢያት በሀብተ ትንቢት በመንፈሰ ትንቢት ‹‹እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት›› /መዝ. 117፥24/ በማለት ትንቢት የተናገሩላት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ትላልቅ የተባሉ ምሥጢራት የተፈጸሙባት ዕለት ናት፡፡

እኔስ በምግባሬ ደካማ ሆኛለሁ


እኔስ በምግባሬ ደካማ ሆኛለሁ
እዘኝልኝ ድንግል ተማጽኜሻለሁ
ነገረ ማርያም/ክፍል አንድ/
«አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ፤»  መኃ 4:7
የትንቢተ ነቢያት ማረፊያ ፡-የስብከተ ሐዋርያት መነሻ.የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ነገረ ማርያም ነው፡፡ ያለ ነገረ ማርያም ነገረ ክርስቶስን መናገር አይቻልም፡፡ በክርስትና ሃይማኖት ታሪክ የተነሡ አያሌ መናፍቃን የመጀመሪያ ችግራቸው የነገረ ማርያምን አማናዊ ትምህርት መቀበል ነበር ፡፡ ያም ችግራቸው ክርስቶስን በትክክል እንዳያምኑት አድርጓቸዋል፡፡ በነገረ ማርያም ላይ የተጣራ ትምህርትና እምነት ቢኖራቸው ኖሮ ለኑፋቄ አይጋለጡም ነበር ፡፡ ንስጥሮስ፡- «አምላክ ወልደ አምላክ» ብሎ በክርስቶስ ለማመን የተሳነው « ወላዲተ አምላክ . ወላዲተ ቃል. እመ እግዚአብሔር » ብሎ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ለማመን በመቸገሩ ነበር፡፡