ክፍል ፭
‹‹አትግደል።›› ዘጸ 20፡13፡፡
አባትና እናትን አለማክበር፣ ሰንበትን አለማክበር፣ ጥንቆላ… በሞት ያስቀጡ ነበር፡፡ ዘሌዋ 20፡10-16፣ ዘሌዋ 21፡14-29፣ ዘጸ 31፡14፣ ዘጸ 22፡20፣ ዘሌዋ 24፡16፣ ቀዳ ነገ 18፡40፣ ዘሌዋ 20፡27፣ ዘጸ 21፡16፡፡ በብሉይ የገደለ እንዲገደል ታዞ ነበር፡፡ ዘፍጥ 9፡6፣ ሮሜ 13፡14፡፡ በሐዲስ ግን እንዲህ አይደለም፡፡ ማቴ 26፡52፡፡ ለእንስሳትና ለሌሎች ፍጥረታትም የሚጎዱን እስካልሆኑ ድረስ እንራራላቸው ዘንድ ይገባናል፡፡ ማቴ 10፡29፡፡ በምንሠራው በእያንዳንዱ ኃጢአት ሰውን ቅር የምናሰኝ ብንሆንም መግደል ግን ሰውን በዚህ ዓለም የተሰጠውን የመኖር ዕድል እንዳይጠቀምበት
የምናደርግበት ኃጢአት ነው፡፡ ይልቁኑ ንስሐ ያልገባን ሰው መግደል እጅግ የሚበዛ በደል ነው መልካምነት የበዛላቸውን ሰዎች መግደል ኅብረተሰቡን መግደል ነው፡፡ … እንዲህ ባለ መንገድ የሚበድሉትንም እግዚአብሔር ይበቀላል፡፡
ራእ 6፡10፡፡ አትግደል የሚለው ሕግ ራስህንም ሆነ ሌላውን አትግደል ማለት ሲሆን አውዳሚ መሳሪያዎችን መጠቀምም በዚህ ሕግ የተከለከለ ነው፡፡ ችሎታችንን፣ እውቀታችንን፣ … ብቃታችንን ሁሉ ሰውን ለሚያጠፋ ምክንያት መጠቀም በዚህ ሕግ የተከለከለ ነው፡፡ ከፍ ባለ አደጋ ጊዜ ግን ራስን መከላከል አልተከለከለም፡፡ በዓለማችንም ሕግ በጦርነት ጊዜ ሕጻናት፣ ሴቶችን፣ አብያተ ክርስቲያናትን፣ ካህናትን፣ መነኮሳትን፣ ሕሙማንን መጉዳትም አልተፈቀደም፡፡ ይህም ዓለማችንን ከጭካኔ ድርጊት ለመታደግ የተደረገ ነው፡፡ በርግጥ ገዳዮች የሚደነቁበት የሚፈሩበት አጋጣሚ ቢኖርም የወንድሞቻቸው ገዳዮች ናቸው፡፡
