ሰባተኛ ትእዛዝ
‹‹አትስረቅ።›› ዘጸ 20፡15፣
ዘዳግ 5፡19፡፡
‹‹ወይም
ሌቦች
ወይም
ገንዘብን
የሚመኙ
ወይም
ሰካሮች
ወይም
ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት
አይወርሱም።›› ቀዳ ቆሮ 6፡10፡፡
ሌብነት ምንድር ነው? የምንሰርቀውስ
ከማን ነው?
ሌብነት
የአንዱን
ሰው
ንብረት
መካፈል
ማለት
አይደለም፡፡ ‹‹በዚያን
ጊዜ
ኢየሱስ
በሰንበት
ቀን
በእርሻ
መካከል
አለፈ፤
ደቀ መዛሙርቱም ተራቡና እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር። ፈሪሳውያንም አይተው። እነሆ፥ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት ማድረግ
ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ አሉት።›› ማቴ 12፡1-2፡፡ እንዳለው ደቀ መዛሙርቱን ጌታችን ሲገስጻቸው አልተመለከትንም፡፡ ይህም
የተራበ ሰው በጎዳናው ያገኘው እሸት ቢኖር ከዚያ ቀጥፎ ከረሐቡ እንዲታገስለት ማድርግ የተፈቀደ መሆኑን ያመለክታል፡፡
‹‹ወደ ባልንጀራህ ወይን ቦታ በገባህ ጊዜ እስክትጠግብ ድረስ ከወይኑ ብላ ወደ ዕቃህ ግን ከእርሱ ምንም አታግባ። ወደ ባልንጀራህ እርሻ
በገባህ ጊዜ እሸቱን በእጅህ ቀጥፈህ ብላ ወዳልታጨደው ወደ ባልንጀራህ እህል ግን ማጭድ አታግባ።›› ዘዳግ 23፡24-25፡፡
በባለቤቱ ፈቃድ ተካፍለን ወስደን እንደሆነ ይህ ሌብነት አይባልም፡፡
የተወሰደበት ሰው ሳያውቅ - ይሁዳ
ደቀ
መዛሙርቱ
ሳያውቁ
ለራሱ
እንደወሰደው ወይም ቤቶችን ሰብረው በመግባት ሌቦች
እንደሚያደርጉት ያለ
ድርጊት
ሌብነት
ይባላል፡፡ ‹‹ይህንም
የተናገረ
ሌባ
ስለ
ነበረ
ነው
እንጂ
ለድሆች
ተገድዶላቸው አይደለም፤
ከረጢትም ይዞ በውስጡ ከሚገባው ይወስድ ስለ ነበረ ነው።›› ዮሐ 12፡6፣ ‹‹ሌቦችም
ቆፍረው
በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ
መዝገብ አትሰብስቡ፡፡›› ማቴ 6፡19፡፡



